የዋጋ ንረትን በተመለከተ
መንግስት በከፍተኛ ሁኔታ ድጎማ በማድረግ የዋጋ ንረቱ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች እንዳይጎዳ በጥንቃቄ እየሰራ ነው። ለአብነትም መንግስት በአንድ ኩንታል ማዳበሪያ 3 ሺህ 700 ብር ይደጉማል። ለነዳጅም 72 ቢሊዮን ብር ተደጉሟል። በዚህም በሊትር 28 ብር እንደጉማለን። የደሞዝ ጭማሪ በማድርግም ቋሚ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ገቢያቸው እንዲያድግ እየተሰራ ነው። ይህ ስራም ተጠናክሮ ይቀጥላል።